top of page
Search

ምባቶማ አክሽን ኢንተርናሽናል ፎረም ከአባላቱና ደጋፊዎቹ $4,750 ዶላር ...

  • Writer: kambattomai
    kambattomai
  • Jun 17, 2022
  • 1 min read

የጎጎታ ኬርን 25ኛ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ ከምባቶማ አክሽን ኢንተርናሽናል ፎረም ከአባላቱና ደጋፊዎቹ $4,750 ዶላር አሰባስቦ እንደነበር ይታወቃል።

ገንዘቡን ለማስተላለፍ አስፈላጊ የሆኑ ሕጋዊና ሌሎች የአሰራር ደንቦች ተጠናቅቀው የተሰበሰበዉ ገንዘብ ኖቬምበር 5, 2021 ዱራሜ ወደሚገኘዉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የጎጎታ ኬር አካውንት ተላልፏል። ከ$4750 ዉስጥ $45.00 ገንዘቡን ላስተላለፈው ባንክ የአገልግሎት ክፍያ ተቆርጦ ቀሪው $4,705.00 ዶላር ለጎጎታ ኬር ተላልፏል። በደረሰኞቹ ላይ የተደለዘዉ ገንዘቡን ያስተላለፈችው የከምባቶማ ገንዘብ ያዥ (treasurer) የግል ኢንፎርሜሽን ነው። የተላከዉ ገንዘብ በዞኑ አካባቢዎች ለሚገኙ ት/ቤቶች የReference መፅሃፍት መግዣ እንደሚውል ከጎጎታ ኬር አመራር ጋር የተወያየን ሲሆን 7ቱም ት/ቤቶች ተለይተው ታውቀዋል። ገንዘቡን ለለገሳችሁ ወገኖች በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ከሁሉም በላይ ሕዝባችን ያመሰግናችኋል። ከምባቶማ አክሽን ኢንተርናሽናል ፎረም።

 
 
 

Recent Posts

See All
KAIF's Open Letter to South African Government

በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ አፍሪካውያንና ኢትዮጵያውያን ወገኖች ላይ እየተካሄደ ያለው የጥላቻ፤ የጥቃት፤ የዘረፋ፤ የንብረት ቅሚያና ግድያ ተግባሮች እንድቆሙ፤ ይህን ድርጊት የሚመሩ ቡድኖችና ግለሰቦች በሕግ እንድጠየቁ፤ እንዲሁም የሲሪል ራማፎሳ መንግሥት በአስቸኳይ የሕግ የበላይነትን እንዲያስከብር ጥሪ የሚያደርግ ግልጽ

 
 
 

Comments


Post: Blog2_Post
bottom of page